በደጃዝማች ኢንዳስትሪያል ኮሌጅ የሶስተኛ ዙር ብቃት የወጣቶች ስራ ላይ ልምምድ የኮምፒተር ክህሎት ስልጠና ወስደው ላጠናቀቁ ወጣቶች የእውቅና ሰርተፊኬት ተሰጠ ።
ለ አምስት ተከታታይ ቀናት ለ 319 ወጣቶች ሲሰጥ የቆየውን ብቃት የወጣቶች ስራ ላይ ልምምድ የኮምፒተር ክህሎት ስልጠና ( Digital Training) መጠናቀቁን ተከትሎ በዛሬው ቀን ስልጠናውን ላጠናቀቁ ወጣቶች የዕውቅና ሰርተፊኬት ተበርክቶላቸዋል ።
በዕውቅና መርሀ ግብሩ የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ በዋናነት 12 ክፍል ያጠናቀቁ እና ከዚያ በታች ሆነው ትምህርት ላይ ያልሆኑ እና ስራ የሌላቸው ወጣቶች ያካተተ ሲሆን ስልጠናውም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል እና ወጣቶቹ በተሰማሩበት የስራ መስክ ተወዳዳሪ ፣ ራሳቸው ስራ ፈጣሪና የስራ ባለ ቤት ለማድረግ በመንግስት የሚመቻችላቸውን እድል በአግባቡ መጠቀም እንዳለባቸው ተገልፀዋል ።
ነሀሴ 23 ቀን ፣ 2017 ዓ/ም
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
.